የክልሉ ዋና ኦዲተር መ/ቤት የሚሰጣቸው አገልግሎቶች
የክልሉን መንግስት መ/ቤቶችንና ድርጅቶችን ሂሣብ ኦዲት ያደርጋል፣ ያስደርጋል፤
የክልሉ መንግስት መ/ቤቶችና ድርጅቶች ያስገኙት ውጤት ህጉን የተከተለ፤ ኢኮኖሚያዊ በሆነ አሠራር የተፈጸመ መሆኑንና ተፈላጊውን ግብ መምታቱን ለማረጋገጥ የክዋኔና የአከባቢ ጥበቃ ኦዲት ያደርጋል፤ ያስደርጋል፡፡
የክልሉ መንግስት መ/ቤቶችና ድርጅቶች አጠቃላይ የቁጥጥር ስርዓት በበቂ ሁኔታ መነደፉንና በትክክለኛ መንገድና በብቃት ተግባራዊ መሆኑን ለማረጋገጥ የሀብት ቁጥጥር ኦዲት ያደርጋል፤ ያስደርጋል፡፡
በመደበኛ ኦዲት ወቅት የአሰራር ግድፈት ወይም ጉድለት ከመገኘቱ የተነሣ አንድ ሂሣብ በልዩ ሁኔታ ኦዲት እንዲደረግ በምክር ቤቱ፤ በክልል ፍ/ቤቶች እና በሌሎች የመንግስት መ/ቤቶችና ድርጅቶች አማካኝነት የተጠየቀ እንደሆነ በጉዳዩ ክብደት ላይ ተመስርቶ የእቅዱ አካል በማድረግ ልዩ ኦዲት ያደርጋል፡፡
የኦዲት ውጤቱ ከፍተኛ ጉድለት መከሰቱንና ወንጀል መፈፀሙን የሚያሣይ ሆኖ ሲገኝ ይህንኑ ለክልሉ ፍትህ ቢሮ፣ለክልሉ መስተዳድር ም/ቤትና ለሥነ-ምግባርና ፀረ ሙስና ኮሚሽን ይልካል፡
ጉዳዩ ከሚመለከታቸው መ/ቤቶችና ድርጅቶች እንዲሁም ከፌደራልና ከክልል ኦዲት መ/ቤቶች ጋር በመመካከር የኦዲት ደረጃ /ስታንዳርድ/ የአሰራር መወሠኛ መመሪያዎች ያወጣል፣
የክልሉ መንግሥት መ/ቤቶችና ድርጅቶች የገንዘብና ንብረት ሂሣብ አያያዝና አጠባበቅ አስመልክቶ በሚያዘጋጀው ማንኛውም ህጎች፡ደንቦችና መመሪያዎች ረቂቅ ሥራ ላይ አስፈላጊውን ምክርና አስተያየት ይሰጣል፣
የግል ኦዲተሮችንና የሂሣብ አያያዝ ባለሙያዎችን የብቃት ማረጋገጫ የምስክር ወረቀት ለመስጠት ፣ ለማገድና ለመሠረዝ የሚያስችልና ወጥነት ያለው መመሪያ ያወጣል፡፡
የምስክር ወረቀቶችን በሚሰጥበትና በሚያድስበት ጊዜ በዚህ አዋጅ መሠረት በሚወጣ ደንብ የሚወሰነውን የአገልግሎት ዋጋ ያስክፍላል፡፡
ኃላፊነቱን በተሟላ ሁኔታ ለመወጣት ይቻለው ዘንድ መጽሐፎችን፡ መዘክሮችን፡ መዝገቦችን፡ ሠነዶችንና ሌሎች መረጃዎችን ለመመልከትና አስፈላጊ ሆኖ ሲያገኘው ከህዝብ አገልግሎት ሰጭ ተቋማት መረጃዎችን ዘገባዎችንና ትንተናዎችን ጠይቆ መቀበል ይችላል፡፡
የመ/ቤቱ ኦዲተሮች ሊከተሉት የሚገባውን ዝርዝር የሙያ ሥነ- ምግባር መመሪያ ያዘጋጃል፡፡
ኢትዮጵያ የህዝብ ፋይናንስ አስተዳደርን ለማሻሻል በተዘጋጀው የሳድኮፓክ ጉባኤ እየተሳተፈች ነው!
ኢትዮጵያ የህዝብ ፋይናንስ አስተዳደርን ለማሻሻል በተዘጋጀው የሳድኮፓክ ጉባኤ እየተሳተፈች ነው ፌዋኦ፣ ጥቅምት 18/2018፡- የደቡባዊ አፍሪካ ልማት ማህበረሰብ የህዝብ ፋይናንስ ኮሚቴዎች ድርጅት (SADCOPAC) 17ኛው አመታዊ ኮንፈረንስ…
የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል መንግስት ዋና ኦዲተር መ/ቤት በበጀት ዓመት አንደኛ ሩብ ዓመት የተመዘገቡ አበረታች ውጤቶች ተጠናክሮ መቀጠል አለባቸዉ ፦ ክብርት ዋና ኦዲተር ወ/ሮ እናትነሽ ማሩ!
የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል መንግስት ዋና ኦዲተር መ/ቤት በበጀት ዓመት አንደኛ ሩብ ዓመት የተመዘገቡ አበረታች ውጤቶች ተጠናክሮ መቀጠል አለባቸዉ ፦ ክብርት ዋና ኦዲተር ወ/ሮ እናትነሽ ማሩ…
መተከል ዞን ሥር ተሰማርተዉ የኦዲት ሥራ እየሰሩ ያሉ የመስክ ኦዲተሮች የክትትልና ድጋፍ ሥራዎች ተጠናክሮ መቀጠል አለበት ፦ ክብርት ዋና ኦዲተር ወ/ሮ እናትነሽ ማሩ
መተከል ዞን ሥር ተሰማርተዉ የኦዲት ሥራ እየሰሩ ያሉ የመስክ ኦዲተሮች የክትትልና ድጋፍ ሥራዎች ተጠናክሮ መቀጠል አለበት ፦ ክብርት ዋና ኦዲተር ወ/ሮ እናትነሽ ማሩ ( መተከል…









